የሀገር ውስጥ ዜና

የጥምቀት በዓል በዩኔስኮ የማይዳሰስ ቅርስ ሆኖ እንዲመዘገብ ተወሰነ

By Tibebu Kebede

December 17, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 2፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የጥምቀት በዓል የማይዳሰስ ቅርስ ሆኖ እንዲመዘገብ መወሰኑን በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) አስታወቀ።

ዩኔስኮ በኮሎምቢያ ቦጎታ በቅርስ ጥበቃ ዙሪያ እያካሄደ ባለው ስብሰባ ነው በኢትዮጵያ የጥምቀት በዓል አከባበር የማይዳሰስ ቅርስ ሆኖ እንዲመዘገብ ውሳኔ ያሳለፈው።