ኢትዮጵያ ለሶማሊያ ህዝብ 15 ቶን ለኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መከላከል የሚውል የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገች

By Tibebu Kebede

June 17, 2020

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ ለሶማሊያ ህዝብ 15 ቶን የሚያወጣ ለኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ እና ሌሎች በሽታዎች መከላከል የሚውል ድጋፍ አደረገች።

ግማሽ ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር የሚያወጣው ይህ ድጋፍ የህክምና ቁሳቁስና መድኃኒቶችን ያካተተ ነው።