ቢዝነስ

የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት 150 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር የገንዘብ ድጋፍ አፀደቀ

By Tibebu Kebede

December 17, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 2፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት የአቅም ግንባታ እና ስልጠና የሚውል 150 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር የገንዘብ ድጋፍ አፀደቀ፡፡

ይህ የገንዘብ ድጋፍ ደረጃውን የጠበቀ ደረጃ ሶስት የባዮሴፍቲ ቤተ ሙከራ ከተሟላ መሳሪያ ጋር ለመገንባት፣ በሁሉም ክልሎች እና ከተማ መስተዳድሮች የሚገነባ 15 ደረጃ ሁለት የባዮሴፍቲ ቤተ ሙከራ ከተሟላ መሳሪያ ጋር ለመገንባት፣ በክልል እና በከተማ መስተዳድር የሚገኙ 8 ቤተ ሙከራዎችን ሙሉ መሳሪያ ለማሟላት ይውላል ተብሏል።