የሀገር ውስጥ ዜና

የአማራ ክልል የከተሞች የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በጎንደር ከተማ ተጀመረ

By Tibebu Kebede

June 18, 2020

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአማራ ክልል የከተሞች የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ዛሬ በጎንደር ከተማ ተጀምሯል።

በክልሉ በሚገኙ ከተሞች በክረምቱ ወራት 165 ሚሊየን ችግኞች የሚተከሉ ሲሆን፥ ዛሬ በጎንደር ከተማ በተጀመረው የተከላ መርሐ ግብርም 20 ሺህ ችግኞች ተተክለዋል።