የሀገር ውስጥ ዜና

“ዴክሳሜታሰን” መድሃኒት ላይ ኢትዮጵያ ተጨማሪ ጥናቶችና ምክሮችን እያሰባሰበች መሆኑ ተገለፀ

By Tibebu Kebede

June 18, 2020

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) “ዴክሳሜታሰን” የተባለው መድሃኒት በኮሮና ቫይረስ በፅኑ የታመሙትን ሰዎች ህይወት ለመታደግ ይረዳል መባሉን ተከትሎ ኢትዮጵያ ተጨማሪ ጥናቶች እና ምክሮችን እያሰባሰበች መሆኑን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።

ከቀናት በፊት የብሪታኒያ ተመራማሪዎች በአነስተኛ ዋጋ በስፋት የሚገኘው “ዴክሳሜታሰን” የተባለው መድሃኒት በኮሮና ቫይረስ በፅኑ የታመሙት ሰዎች ላይ የሚከሰት የሞት መጠንን እንደሚቀንስ መግለፃቸው ይታወሳል።