ቢዝነስ

ምርት ገበያው በህዳር ወር 2 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ዋጋ ያላቸውን ምርቶች አገበያየ

By Tibebu Kebede

December 17, 2019

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 2 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ምርት ገበያ በህዳር ወር 2 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ዋጋ ያላቸውን 60 ሺህ 825 ቶን ምርቶች ማገበያየቱን አስታወቀ።

ምርት ገበያው ለጣቢያችን በላከው መግለጫ በህዳር ወር ከተገበያዩት ምርቶች ውስጥ ቡና 36 በመቶ የግብይት መጠንና 50 በመቶ የግብይት ዋጋ በማስመዝገብ ቀዳሚ መሆኑን አስታውቋል።