አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 12 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ዴክሳሜታዞን የተባለውን መድሀኒት ኦክሲጅን ወይም የመተንፈሻ መሳሪያ እገዛ ለሚያስፈልጋቸው የኮቪድ-19 ህሙማን የህክምና ባለሙያዎች በሚያዙት መሰረት እንደ ድንገተኛ ህክምና ለመጠቀም መወሰኑን የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታወቁ፡፡
ሚኒስትሯ በፌስ ቡክ ገፃቸው እንዳስታወቁት ለኮቪድ-19 ህሙማን የሚውለውን ዴክሳሜታዞን የተባለውን መድሀኒት በተመለከተ በእንግሊዝ መንግስት የተካሄደውን ጥናት እና ሪፖርት በዝርዝር ተመልክተዋል፡፡