የሀገር ውስጥ ዜና

የጥምቀት በዓል የዓለም ቅርስ ሆኖ በዩኔስኮ በመመዝገቡ ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ገለፀች

By Tibebu Kebede

December 17, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 2፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የጥምቀት በዓላል የዓለም ቅርስ ሆኖ በዩኔስኮ በመመዝገቡ ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ገለፀች።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርቲያን ፓትሪያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ የጥምቀት በዓል በዩኔስኮ ከማይዳሰሱ የዓለም ቅርሶች መካከል አንዱ ሆኖ መመዝገቡን አስመልክተው ከሰዓቱን መግለጫ ሰጥተዋል።