ቢዝነስ

ባለፉት አራት ወራት ከወጪ ንግድ 916 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ገቢ ተገኘ

By Tibebu Kebede

December 17, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 3፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2012 በጀት ዓመቱ አራት ወራት ከግብርና፣ ከማምረቻ እና ከማዕድን ምርቶች ዘርፍ 916 ነጥብ 21 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ተገኘ፡፡

በበጀት ዓመቱ አራት ወራት 1 ነጥብ 07 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ ነው 916 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ገቢ መገኘቱ የተገለፀው፡፡