የሀገር ውስጥ ዜና

ምክር ቤቱ የ2012 በጀት ዓመት የስራ ግምገማ እያካሄደ ነው

By Tibebu Kebede

June 24, 2020

አዲስ አበባ ፣ሰኔ 17፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሚኒስትሮች ምክር ቤት የ2012 በጀት ዓመት የስራ ግምገማ እያካሄደ ይገኛል።

በትናንትናው ዕለት የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች ከኢኮኖሚ አኳያ ያከናወኗቸውን ተግባራት ማቅረባቸው የሚታወስ ነው።

በዛሬው ዕለትም በማኅበራዊው ዘርፍ የተሠማሩት የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች ካወጧቸው መሥፈርቶች አንጻር ክንውናቸውን እያቀረቡ እንደሚገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በፌስቡክ ገፃቸው ላይ አስፍረዋል።