የሀገር ውስጥ ዜና

በጋምቤላ ክልል ለስድስት ዓመታት ተግባራዊ የሚደረግ የቆላማ አካባቢ ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት ይፋ ሆነ

By Tibebu Kebede

June 24, 2020

አዲስ አበባ ፣ሰኔ 17፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በጋምቤላ ክልል ለስድስት ዓመታት በስምንት ወረዳዎች ተግባራዊ የሚደረግ የቆላማ አካባቢ ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት ይፋ ሆነ፡፡

ፕሮጀክቱ የክልሉን ህብረተሰብ የልማት ፍላጎት ለማሳካት የሚያስችል ፕሮጀክት መሆኑን የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ ገልፀዋል፡፡