የ114 የእድሜ ባለፀጋ ከኮሮና ቫይረስ ሙሉ በሙሉ አገግመው ከኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ወጡ
አዲስ አበባ ፣ሰኔ 17፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የ114 የእድሜ ባለፀጋ ከኮሮና ቫይረስ ሙሉ በሙሉ አገግመው ከኤካ ኮተቤ ሆስፒታል መውጣታቸው ተገለፀ።
አዛውንቱ ለተጨማሪ ህክምና የካቲት 12 ሆስፒታል እንደሚገኙ የሆስፒታሉ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር ያሬድ አግደው በፈስቡክ ገፃቸው ላይ አስፍረዋል።
ዋና ስራ አስፈፃሚው አዛውንቱ በአሁኑ ሰዓት በጥሩ ጤንነት ላይ እንዲመገኙም በመግለፅ ለዚህ ስኬትም ለጤና ባለሞያዎች ምስጋና አቅርበዋል።
#FBC
የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዘናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።