የሀገር ውስጥ ዜና

ኢንጂነር ታከለ ኡማ ከቻይና ኢኮኖሚና ንግድ ጉዳዮች አማካሪ ከሆኑት ሊው ጋር ተወያዩ

By Tibebu Kebede

December 17, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ከቻይና ኢኮኖሚና ንግድ ጉዳዮች አማካሪ ከሆኑት ሊው ጋር ተወያዩ።

በውይይታቸውም በቅርቡ ጎተራ አከባቢ ስለሚጀመረው ዘመናዊ የመኖሪያ መንደር ግንባታ ዙሪያ መክረዋል።