የሀገር ውስጥ ዜና

በዶሃ ፎረም በመሳተፍ ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ልኡክ የኢትዮጵያ ኮሚዩኒቲ ዓለም አቀፍ ት/ቤትን ጎበኘ

By Tibebu Kebede

December 17, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዴሪ የሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ከሚል፣ የቀድሞው የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ እንዲሁም የኢጋድ ዋና ጸሐፊ ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ በፈረንጆቹ ከታህሳስ 14 አስከ 15 በኳታር በሚካሄደው 19ኛው የዶሃ ፎረም ላይ ለመሳተፍ ዶሃ ገብተዋል።

ከፎረሙ አስቀድሞም የሰላም ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ከሚል እና የቀድሞው የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በዛሬው እለት በዶሃ የኢትዮጵያ ኮሚዩኒቲ ዓለም አቀፍ ት/ቤትን ጎብኝተዋል።