የሀገር ውስጥ ዜና

በአስገድዶ መድፈር ወንጀል የተከሰሱ ግለሰቦች ከ11 እስከ 25 ዓመት በሚደርስ እስራት ተቀጡ

By Feven Bishaw

June 26, 2020

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 19፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአስገድዶ መድፈር ወንጀል የተከሰሱ ግለሰቦች በ25 እና በ በ11 ዓመት ከ9 ወር ፅኑ እስራት ተቀጡ፡፡

የ64 ዓመቱ ተከሳሽ ነሐሴ ወር 2011 ዓ.ም በአዲስ አበባ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ዕድሜያቸው ስምንት እና ዘጠኝ አመት የሆኑ ሁለት ሴት ህፃናቶችን በተለያዩ ቀናቶች ተከራይቶ ከሚኖርበት ቤት ውስጥ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ፈጽሞባቸዋል፡፡