አዲስ አበባ፣ ሰኔ 19፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች እና የልማት ማዕከል (ኢ ሲ ዲ ዲ) ጋር በመተባበር ድጋፍ የአካል ጉዳተኞች የኮሮና ወረርሽኝን ለመከላከል የሚያግዝ 320 ሺህ ብር የሚገመት የንፅህና መጠበቂያ እና የምግብ ግብዓት ድጋፍ አድርገዋል፡፡
በዚህም ለችግር ተጋላጭ ለሆኑ 200 አካል ጉዳተኞች የምግብ ግብዓትና የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁስ ድጋፍ የተደረገ ሲሆን ለ400 አካል ጉዳተኞች የሚሆን የንፅህና መጠበቂያ እና የፊት ማስክ የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ብሔራዊ ማህበር ፌዴሬሽን ተረክቧል፡፡