የሀገር ውስጥ ዜና

የኩፍኝ በሽታ የክትባት ዘመቻ ሊካሄድ ነው

By Feven Bishaw

June 29, 2020

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ የኩፍኝ በሽታ የክትባት ዘመቻ ከሰኔ 23 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ እንደሚካሄድ አስታወቀ፡፡

ቢሮው ዘመቻውን አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ እድሜያቸው ከ9 ወር እስከ 5 አመት ለሆናቸው ህፃናት ከሰኔ 23 ቀን እስከ ሐምሌ 2 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ ክትባቱ ይሰጣል ብሏል፡፡