የሀገር ውስጥ ዜና

ጃፓን በኢትዮጵያ ኮቪድ19ን ለመከላከል የሚውል 4 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ አደረገች

By Feven Bishaw

June 29, 2020

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጃፓን የመንግስታቱ ድርጅት የህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) በኢትዮጵያ የኮቪድ19 ወረርሽኝ ተፅዕኖን ለመከላከል የሚያደርገውን ጥረት ለማገዝ የሚውል 4 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ለገሰች።

ድጋፉ የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ለመከላከል የሚያግዙ የኢንፌክሽን መከላከያ፣ የመጠጥ ውሃና የስነ ንጽህና እንዲሁም የጤና ባለሙያዎችን አቅም ማሳደግ የሚያስችል ነው ተብሏል።