አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጃፓን የመንግስታቱ ድርጅት የህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) በኢትዮጵያ የኮቪድ19 ወረርሽኝ ተፅዕኖን ለመከላከል የሚያደርገውን ጥረት ለማገዝ የሚውል 4 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ለገሰች።
ድጋፉ የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ለመከላከል የሚያግዙ የኢንፌክሽን መከላከያ፣ የመጠጥ ውሃና የስነ ንጽህና እንዲሁም የጤና ባለሙያዎችን አቅም ማሳደግ የሚያስችል ነው ተብሏል።