የሀገር ውስጥ ዜና

ሚኒስቴሩ የኮቪድ19ኝን ተፅዕኖ ለመቋቋም ለአቅመ ደካሞችና ጧሪ ለሌላቸው አረጋውያን ድጋፍ አደረገ

By Feven Bishaw

June 29, 2020

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ትምህርት ሚኒስቴር የኮቪድ 19ኝን ተፅዕኖ ለመቋቋም እንዲረዳ ለአቅመ ደካሞችና ጧሪ ለሌላቸው አረጋውያን ድጋፍ አደረገ፡፡

ድጋፉ የተደረገው በአራዳ ከፍለ ከተማ ወረዳ 9 አስተዳደር ሲሆን የምግብ እህል፣ የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁስና አልባሳትን ያካተተ ሲሆን በትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞች ወጪ የተሸፈነ ነው ተብሏል።