የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብጽ ልዩነታቸውን በውይይት እንዲፈቱ ቻይና ድጋፏን አጠናክራ እንደምትቀጥል አስታወቀች

By Feven Bishaw

June 29, 2020

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከቻይና ስቴት ካውንስልና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ጋር የስልክ ውይይት አድርገዋል።

ሚኒስትሮች በነበራቸው የስልክ ውይይት በሁለትዮሽ እና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ዙሪያ ሁለቱ ሃገራት ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ማጠናከር በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል።