የሀገር ውስጥ ዜና

የሕዳሴ ግድብ በደለል እንዳይሞላ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራው ተጠናክሮ መቀጠል አለበት – ኢንጂነር ስለሺ በቀለ

By Feven Bishaw

June 29, 2020

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በደለል እንዳይሞላ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራው ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጅነር ስለሺ በቀለ አሳሰቡ።

የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤትና የተጠሪ ተቋማት ሠራተኞች በሱሉልታ ወረዳ ደርባ ከተማ አካባቢ የአረንጓደ አሻራቸውን አሳርፈዋል።