የሀገር ውስጥ ዜና

በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ ልዑክ በስደተኞች ፎረም ላይ እየተሳተፈ ይገኛል

By Tibebu Kebede

December 17, 2019

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 6 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የተመራ የመንግስት ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በዓለም አቀፉ የስደተኞች ፎረም ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ጄኔቫ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በኢትዮጵያ ሚሲዮን አመራሮች አቀባበል ተደርጎላቸዋል።