የሀገር ውስጥ ዜና

በአማራ ክልል በመኸር ከተዘራው ሰብል ውስጥ ከ3 ሚሊየን ሄክታር በላይ ተሰብስቧል

By Tibebu Kebede

December 17, 2019

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 6 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል በሰብል ከተሸፈነው 4 ነጥብ 2 ሚሊየን ሄክታር መሬት ውስጥ እስካሁን 3 ነጥብ 1 ሚሊየን ሄክታሩ መሰብሰቡን የክልልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

የክልሉ ግብርና ቢሮ ሃላፊዎችና ሰራተኞች በዛሬው እለት በባህርዳር ዙሪያ ወረዳዎች የአቅመ ደካማና ሴት አርሶ አደሮችን ሰብል በዘመቻ ሰብስበዋል።