ቢዝነስ

የእርግብ አተር፣ ቀይ ዥንጉርጉር ቦሎቄ እና ፒንቶ ቢን የተባሉት ምርቶች ግብይታቸው በምርት ገበያ እንዲሆን ተወሰነ

By Tibebu Kebede

July 20, 2020

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 13፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የእርግብ አተር፣ ቀይ ዥንጉርጉር ቦሎቄ እና ፒንቶ ቢን የተባሉት የግብርና ምርቶች ግብይታቸው በኢትዮጵ ምርት ገበያ ብቻ እንዲፈጸም ተወስኗል፡፡

በ2012 በጀት ዓመት ከወጪ ንግድ ለማግኘት የታቀደው ገቢ ሙሉ በሙሉ ላለመገኘቱ ምክንያት ከሆኑ ጉዳዮች እንዱ የወጪ ንግድ ምርቶች አቅርቦት እጥረት መሆኑን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታውቋል።