ቢዝነስ

ሚድሮክ ኢትዮጵያ ግሩፕ 5 ሊትሩን የምግብ ዘይት በ330 ብር ለሸማቶች ማቅረብ ጀመረ

By Tibebu Kebede

July 20, 2020

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 13፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ሚድሮክ ኢትዮጵያ ግሩፕ የምግብ ዘይት በተመጣጣኝ ዋጋ በአዲስ አበባ ከተማ እያቀረበ ይገኛል።

ግሩፑ መንግስት በምግብ ዘይት ላይ የጣለውን ታክስና ቀረጥ በማንሳቱ 5 ሊትሩን የምግብ ዘይት በ330 ብር ለሸማቶች እያቀረበ እንደሚገኝ ነው የተገለፀው።