Fana: At a Speed of Life!

የቱሪዝም ሚኒስትሯ ሰላማዊት በጋምቤላ ከተማ የቱሪስት መስህቦችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 26፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የቱሪዝም ሚኒስትሯ ሰላማዊት ካሳ በጋምቤላ ከተማ የሚገኙ የቱሪስት መስህቦችን ጎብኝተዋል፡፡

የቱሪዝም ሚኒስትሯ ሰላማዊት ከጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድ ጋር በመሆን ነው በከተማው የሚገኙ የቱሪስት መስህቦችን የጎበኙት፡፡

በጉብኝታቸውም የጋምቤላ ከተማን ለሁለት ከፍሎ የሚያልፈውን ታሪካዊው የባሮ ድልድይን እና ዓመቱን ሙሉ የሚፈሰውን የባሮ ወንዝን መመልከታቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.