Fana: At a Speed of Life!

የተቋረጠውን ኃይል ወደነበረበት ለመመለስ ርብርብ እየተደረገ ነው- አገልግሎቱ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 28፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በመላው ሀገሪቱ የተቋረጠውን ኃይል ወደነበረበት ለመመለስ በኃይል ማመንጫዎች እና በማከፋፈያ ጣቢያዎች ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ገለጸ፡፡

ዛሬ ማምሻውን በሲስተም አለመረጋጋት ምክንያት በተፈጠረ ችግር በመላው ሀገሪቱ የኃይል መቋረጥ እንዳጋጠመ አገልግሎቱ ገልጿል፡፡

ችግሩን በመፍታት የተቋረጠውን ኃይል ወደነበረበት ለመመለስም በኃይል ማመንጫዎች እና በማከፋፈያ ጣቢያዎች ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

የተፈጠረው ችግር እስኪፈታ ድረስ ደንበኞች በትዕግስት እንዲጠብቁ የጠየቀው አገልግሎቱ ያሉትን መረጃዎች በፍጥነት እንደሚያሳውቅም ገልጿል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.