Fana: At a Speed of Life!

የተባበሩት መንግስታት የኢትዮጵያና ሶማሊያን ስምምነት እንደሚደግፍ አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የተባበሩት መንግስታት በኢትዮጵያና ሶማሊያ መካከል በአንካራ የተደረሰውን ስምምነት እንደሚደግፍ አስታውቋል፡፡

የተባበሩት መንግስታት እንዳለው ፥ ስምምነቱ በወዳጅነት እና በእርስ በርስ መከባበር መንፈስ የመጣ እንደሆነም ገልጿል፡፡

በዚህም የተደረሰውን ስምምነት ተግባራዊነት እውን እንደሚሆን የጠቆመ ሲሆን ፥ ለዚህም ስምምነት ትልቁን ድርሻ የተወጣቸውን ተርኪዬን አመስግኗል፡፡

በዚህም የስምምነቱ ትግበራ ላይ የተባበሩት መንግስታት ድጋፍ እንደሚያደርግ ጠቅሶ ፥ ልዩነቶች በንግግር ለመፍታት የፖለቲካ ፍቃደኝነት እንደሚያስፈልግም ነው የተጠቆመው፡፡

በተመሳሳይ ብሪታኒያ ስምምነቱ የኢትዮጵያን እና የሶማሊያን በጋራ የመልማት ፍላጎት እና ቁርጠኝነት ያሳየ ነው በማለት ስምነቱን እንደምትደግፍ የገለጸች ሲሆን ፥ የትርክዬን ሚናም አድንቃለች።

ብሪታኒያ በቀጣናው መረጋጋት፣ ልማት እና ሰላም እንዲሰፍን ከሀገራቱ ጋር በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኗንም አስታውቃለች።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.