Fana: At a Speed of Life!

ከ330 ሚሊየን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች ተያዙ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) 331 ነጥብ 9 ሚሊየን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች መያዙን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

ኮሚሽኑ ከሕዳር 27 እስከ ታሕሳስ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ባደረገው ክትት ነው 308 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር የገቢና 23 ነጥብ 1 ሚሊየን ብር የወጪ ኮንትሮባንድ እቃዎችን የያዘው፡፡

ከተያዙት እቃዎች መካከልም አልባሳት፣ኤሌክትሮኒክስ፣ ወርቅ፣ ቡና፣ ጥራጥሬ፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫ፣ የመዋቢያ እቃዎች፣ አደንዛዥ እጾች ፣ መድኃኒት፣ የተለያዩ ተሽከርካሪዎችና የውጭ ሀገራት ገንዘቦች ይገኙበታል ተብሏል፡፡

ሐዋሳ፣ ሞያሌና ድሬድዋ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ኮንትሮባንድን በመቆጣጠር ረገድ ቀዳሚውን ስፍራ እንደሚይዙ የኮሚሽኑ መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.