ሪያል ማድሪድ የኢንተርኮንቲኔንታል ካፕ ዋንጫን አነሳ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የስፔኑ ክለብ ሪያል ማድሪድ የ2024 የፊፋ ኢንተርኮንቲኔንታል ካፕ ዋንጫን አንስቷል፡፡
ማድሪድ ዋንጫውን ለማንሳት የበቃው ከሜክሲኮው ክለብ ፓቹካ ጋር ያደረገውን የፍፃሜ ጨዋታ 3 ለ 0 በመርታት ነው፡፡
ኪሊያን ምባፔ፣ ሮድሪጎ እና ቪኒሺየስ ጁኒየር ደግሞ ግቦቹን ከመረብ ማሳረፋቸውን ቢቢሲ ስፖርት ዘግቧል፡፡