Fana: At a Speed of Life!

የኦሮሚያ ክልል የህብረተሰብ ወኪሎች የአጀንዳ ማሰባሰብ ምክክር ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኦሮሚያ ክልል የህብረተሰብ ወኪሎች የአጀንዳ ማሰባሰብ ምክክር ምዕራፍ መጠናቀቁን የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አምባዬ ኡጋቶ በሰጡት መግለጫ ÷10 የማህበረሰብ ክፍሎችን ወክለው የተገኙ 7 ሺህ 20 ተወካዮች ለጠቅላላ ጉባኤ የሚሳተፉ 320 ተወካዮችን መርጠዋል ብለዋል፡፡

የማህበረሰብ ተወካዮች የምክክር ሒደት መጀመሪያ የነበረው የመነጋገር ፍላጎት በሚገባ የተንፀባረቀበት መሆኑን አንስተዋል።

በአጀንዳ አሰባሰቡ ያልተገደቡ ውይይቶች መደረጋቸውን ጠቁመው÷ ተዓማኒና ሁሉም የተሳተፍበት እንደነበር አስረድተዋል፡፡

የ320ዎቹ ተወካዮች ምርጫም ክርክር ተደርጎበት ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ መከናነወኑን ነው የገለጹት፡፡

በቀጣዮቹ ቀናት የአጀንዳ መለየትና የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ እንደሚካሄድም ተጠቅሷል፡፡

በአሸናፊ ሽብሩና መራኦል ከድር

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.