ኢትዮጵያና ርዋንዳ ወታደራዊ ትብብራቸውን ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆናቸውን ገለጹ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 16፣ 2017(ኤፍ ኤም ሲ) የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሃመድ (ኢ/ር) ከርዋንዳ አቻቸው ጁቬናል ማሪዛሙንዳ ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም ሀገራቱ በወታደራዊ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር በሚችሉበት ሁኔታ ላይ መክረዋል፡፡
ሁለቱ ወገኖች በቀጣይ ወታደራዊ ትብብራቸውን ይበልጥ ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡