ፕሬዚዳንት ታዬ መቄዶንያ የአረጋውያንና አዕምሮ ሕሙማን መርጃ ማዕከልን ጎበኙ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 18፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ መቄዶንያ የአረጋውያን እና አዕምሮ ሕሙማን መርጃ ማዕከልን ጎብኝተዋል።
መቄዶንያ የአረጋውያንና አዕምሮ ሕሙማን መርጃ ማዕከል በ44 ከተሞች ከ8 ሺህ በላይ ሰዎች ባሕላዊ እና መንፈሳዊ ፍላጎትና ክብራቸው ተጠብቆ እየተረዱ የሚገኙበት ተቋም መሆኑን ኢዜአ ዘግቧል፡፡