422 ሺህ 842 ሰዎች የኮደርስ ስልጠና በመውሰድ ላይ መሆናቸው ተገለጸ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 18፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ5 ሚሊየን ኢትዮጵያዊያን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ 422 ሺህ 842 ሰዎች ስልጠናውን በመውሰድ ላይ መሆናቸውን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ።
ሚኒስትሩ የኢኒሼቲቩን አተገባበር ለመከታተል እና ለመደገፍ ለተቋቋመው ግብረ-ኃይል መመሪያ በሰጡበት ወቅት እንዳሉት÷ እስከ አሁን 104 ሺህ 460 ሰዎች ስልጠናውን አጠናቅቀው የምስክር ወረቀት ወስደዋል።
5 ሚሊየን ኢትዮጵያዊያን የዲጂታል ክኅሎት ስልጠና እንዲወስዱ የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት በየደረጃው ያሉ አመራሮችና ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ በቅንጅት እየተሠራ ነው ማለታቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል።