Fana: At a Speed of Life!

በሰው ሰራሽ አስተውሎት የፖሊዮ መረጃን የሚያሰራጭ መተግበሪያ ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 19፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ሰው ሰራሽ አስተውሎትን በመጠቀም የፖሊዮ መረጃዎችን ተደራሽ ማድረግ የሚያስችል መተግበሪያ ይፋ ተደርጓል፡፡

በኢትዮጵያ ያለውን የፖሊዮ ክትትል ውስንነት መቅረፍ ያስችላል የተባለው “ፖሊዮአንቴና” መተግበሪያ በጅማ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ነው የበለጸገው፡፡

የፖሊዮ አንቴና ፕሮጀክት አስተባባሪ ሁንዴሳ ዳባ÷በተለያዩ አካባቢዎች እየተስተዋለ ያለውን ከክትባትጋር የተላመደ የፖሊዮ በሽታ ለመቆጣጠር መተግበሪያው እገዛ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።

መረጃን ከመሰብሰብ ባሻገር የተሰበሰበውን መረጃ ወደ ሚመለከተው አካል ለማስተላለፍ እንዲሁም ሕመሙ ፖሊዮ መሆን አለመሆኑን ማረጋገጥ ያስችላል ተብሏል።

አሁን ላይ የወባና መሰል ወረርሽኞችን መረጃ ማሰራጨት እንዲሁም በሽታውን መከላከል የሚያስችሉ የሰው ሰራሽ አስተውሎት የሚጠቀሙ መተግበሪያዎች በኢንስቲትዩቱ እየበለጸጉ መሆኑም ተመላክቷል።

በወርቃፈራው ያለው እና አቤኔዘር ታዬ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.