ኦሊጎነር ሶልሻየር የቤሽክታሽ አሰልጣኝ ሆነ
አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ)የቀድሞው የማንቸስተር ዩናይትድ ተጫዋች ኦሊጎነር ሶልሻየር የቤሺክታሽ እግር ኳስ ቡድን አሰልጣኝ ሆኖ ተሾመ።
ሶልሻየር የቱርኩን እግር ኳስ ቡድን እስከ 2026 ለማሰልጠን መስማማቱን የተረጋገጡ የዝውውር መረጃዎችን የሚያወጣው ፋብሪዚዮ ሮማኖ በፌስ ቡክ ገፁ አስፍሯል።
ኦሊጎነ ሶልሻየር በማንቸስተር ዩናይትድ ከሁለት ዓመት ተኩል ስኬታማ የተጫዋችነት ዘመን በተጨማሪ እ.ኤ.አ ከ2019 እስከ 2021 በአሰልጣኝነት መርቷል።