Fana: At a Speed of Life!

ቅዱስ ጊዮርጊስ እና አርባ ምንጭ ከተማ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል

አዲስ አበባ፣ ጥር 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 15ኛ ሣምንት መርሐ-ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ ድሬዳዋ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በአዳማ ሣይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ÷ የቅዱስ ጊዮርጊስን ግቦች ኢስማኤል አብዱል ጋንዩ (በራስ ላይ) እና ፍፁም ጥላሁን (በፍፁም ቅጣት ምት) አስቆጥረዋል፡፡

ሁለቱም ግቦች የተቆጠሩት በሁለተኛው አጋማሽ ነው፡፡

በሌላ ጨዋታ ስሑል ሽረ በአርባ ምንጭ ከተማ 1 ለ 0 ተሸንፏል፡፡

ከእረፍት መልስ የተቆጠረችውን የአርባምንጭ ከተማን ግብ ቡታቃ ሸመና ከመረብ ማሳረፍ ችሏል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.