የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ 7ኛ ዙር ጨዋታዎች ዛሬ ይደረጋሉ
አዲስ አበባ፣ ጥር 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአውሮፓ የተለያዩ ከተሞች የሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታዎች ምሽት ላይ ሲደረጉ ቤኔፊካ ከባርሴሎና እንዲሁም አትሌቲኮ ማድሪድ ከባየርሊቨርጉሰን የሚያደርጉት ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
ምሽት 2 ከ45 ላይ ቤርጋሞ ላይ አታላንታ ከስትሩም ግራዝ እንዲሁም ሞናኮ ከአስቶንቪላ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ምሽት 5 ሠዓት ላይ ደግሞ አትሌቲኮ ማድሪድ ከባየርሊቨርጉሰን፣ ቤኔፊካ ከባርሴሎና፣ ቦሎኛ ከቦሩሺያ ዶርቱመንድ፣ ክለብ ብሩጅ ከጁቬንቱስ፣ ሊቨርፑል ከሊል፣ ሬድ ስታር ቤልግሬድ ከፒኤስቪ እንዲሁም ስሎቫን ብራቲስላቫ ከስቱትጋርት ይጫወታሉ፡፡