Fana: At a Speed of Life!

አንዲት በግ አምስት ግልገሎችን ወለደች

አዲስ አበባ፣ ጥር 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በምስራቅ ጎጃም ዞን በደብረ ወርቅ ከተማ አንዲት በግ 5 ግልገሎችን ወልዳለች።

 

የተወለዱት ግልገሎች ሁለቱ ወንዶች ሲሆን ሶስቱ  ሴቶች ናቸው፡፡

 

በጓ ከዚህ በፊትም በአንድ ጊዜ ሶስት እና አራት ግልገሎችን ወልዳ እንደነበር የበጓ ባለንብረት ተናግረዋል።

 

በጓ እና ግልገሎቿም በአሁኑ ሰዓት በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙ የእናርጅ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

 

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.