የሀገር ውስጥ ዜና

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከኢንቨስትመንት እና የሥራ ዕድል ፈጠራ ብሔራዊ ኮሚቴ ጋር ተወያዩ

By Tibebu Kebede

July 27, 2020

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከኢንቨስትመንት እና የሥራ ዕድል ፈጠራ ብሔራዊ ኮሚቴ ጋር ተወያዩ።

የውይይቱ ዓላማም ባለፈው ዓመት የተካሄዱትን ብሔራዊ የሥራ ዕድል ፈጠራ ክንዋኔዎች መመዘን እና ለቀጣዩ ዓመት አቅጣጫ መስጠት መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት አስታውቋል፡፡