Fana: At a Speed of Life!

አርሰናል ማንቼስተር ሲቲን 5 ለ 1 አሸንፏል

አዲስ አበባ፣ ጥር 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ24ኛ ሣምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አርሰናል በኤምሬትስ ስታዲየም ማንቼስተር ሲቲን 5 ለ 1 ረትቷል፡፡

የመድፈኞቹን ግቦች ኦዴጋርድ፣ ፓርቴ፣ ሌዊስ ስኬሊ፣ ሀቨርትዝ እና ንዋኔሪ ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል፡፡

የውኃ ሰማያዊዎቹን ከሽንፈት ያልታደገች ግብ ደግሞ ኤርሊንግ ሃላንድ አስቆጥሯል፡፡

ቀደም ብለው በተካሄዱ የዛሬ መርሐ-ግብሮች ማንቼስተር ዩናይትድ በክሪስታል ፓላስ እንዲሁም ብሬንትፎርድ በቶተንሃም ሆትስፐር በተመሳሳይ ውጤት 2 ለ 0 ተሸንፈዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.