Fana: At a Speed of Life!

እስራኤል በቴክኖሎጂ ዘርፍ ለኢትዮጵያ ድጋፏን እንደምታጠክር ገለጸች

አዲስ አበባ፣ ጥር 28፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ከእስራኤል ኢነርጂና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ኢሊ ኮህን ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም ሀገራቱ በፈጠራ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምርምር፣ ስታርትአፕ ልማትና በሃይል ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡

በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ÷ኢትዮጵያ በዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ፣ በስታርትአፕ ልማት፣ በምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በሃይል አቅርቦትና በግብርና ቴክኖሎጂ ጠንካራ እንቅስቃሴ እያደረገች ነው ብለዋል፡፡

በተለይም ዲጂታል ኢትዮጵያ እውን ማድረግ የሚያስችሉ ሥራዎችን እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመው ÷ እስራኤል በዘርፉ ያላትን ጠንካራ ልምድ በተሞክሮነት የሚወሰድ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

ኤሊ ኮህን በበኩላቸው ÷ በግብርና ቴክኖሎጂ፣ በኢኖቬሽንና በታዳጊ የቴክኖሎጂ መስኮች ያለውን ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ መስራት እንደሚገባ አንስተዋል፡፡

እስራኤል በቴክኖሎጂና በሃይል ያላትን እውቀት በመጠቀም እያደገ የመጣውን የኢትዮጵያ የኢኖቬሽን ሥነ-ምህዳር ለመደገፍና ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል፡፡

ውይይቱ የእስራኤል ባለሃብቶች በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ኢንቨስት እንዲያደርጉ በር የሚከፍት እንደሆነ መናገራቸውንም የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.