አምባሳደር ባጫ ደበሌ ከኬንያ ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 3፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኬንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ባጫ ደበሌ ከኬንያ ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ ጋር ተወያይተዋል፡፡
አምባሳደር ባጫ በናይሮቢ በተዘጋጀውና ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ በተገኙበት ዓመታዊ የዲፕሎማሲ ማብራሪያ መድረክ ላይ ተሳትፈዋል፡፡
ከማብራሪያው ጎን ለጎን አምባሳደር ባጫ ከፕሬዚዳንት ሩቶ ጋር ተገናኝተው መምከራቸውን የኤምባሲው መረጃ አመልክቷል፡፡