የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ም/ቤት መደበኛ ጉባዔ እየተካሄደ ነው
አዲስ አበባ፣ የካቲት 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን፣ 7ኛ መደበኛ ጉባዔ መካሄድ ጀምሯል፡፡
በጉባዔው የአስፈጻሚ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የ6 ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ የሚገመገም ሲሆን÷ ጉባዔው በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ እንደሚያሳልፍም ተመላክቷል፡፡