Fana: At a Speed of Life!

የኢትዮ-ጅቡቲ ኮሪደር አስተዳደር ባለስልጣን የምስረታ መድረክ እየተካሄደ ነው

 

 

አዲስ አበባ፣ የካቲት 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮ-ጅቡቲ ኮሪደር አስተዳደር ባለስልጣን የምስረታ መድረክ በቢሾፍቱ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

 

በመርሐ ግብሩ ላይ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) እንደተናገሩት÷ ኮሪደር አስተዳደር ባለስልጣን መመስረቱ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የመሰረተ-ልማት ዝርጋታን በዘመናዊ መንገድ የቁጥጥር ስርዓት በመታገዝ የተሻለ የንግድ ልውውጥ ለማድረግ ያስችላል።

 

የሁለቱን ሀገራት የንግድ ግንኙነት ይበልጥ በማጠናከር እና በዘርፉ የሚስተዋለውን ህገ-ወጥ ንግዶችን በመቆጣጠር ህጋዊ የንግድ ስርዓት እንዲስፋፋ በማድረግ ረገድ የጎላ አስተዋፅዖ እንዳለው አንስተዋል።

 

የሁለቱን ሀገራት የትራንስፖርት ተቋማት በማቀናጀት ወደ ተሻለ የንግድ ምዕራፍ እንደሚወስድ መናገራቸውንም በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።

 

የጅቡቲ መሰረተ-ልማት እና ኢኪዩፕመንት ሚኒስትር ሀሰን ሀሙድ÷ የጅቡቲ ንግድ እና ቱሪዝም ሚኒስትር መሀመድ ዋርሳማ እና ሌሎች የሁለቱ ሀገራት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በመድረኩ ተገኝተዋል።

 

 

 

 

 

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.