ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) ከአፍሪካ ልማት ባንክና ከአለም የእርሻ ልማት ፈንድ ፕሬዚዳንቶች ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ)ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት አኪንውሚ አደሲና እና ከዓለም የእርሻ ልማት ፈንድ ፕሬዚዳንት አልቫሮ ላሪዮ ጋር ተወያዩ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ለኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ እያደረጉት ባለው ድጋፍ ዙሪያ ከሁለቱ ተቋማት ፕሬዚዳንቶች ጋር መወያየታቸውን በኤክስ ገጻቸው አስፍረዋል።
በኢንዱስትሪው ዘርፍም ቀጣይነት ያለው እድገት እና ችግርን የመቋቋም አቅምን ለማጎልበት ትብብር ስለማሳደግም ተወያይተናል ብለዋል።