የሀገር ውስጥ ዜና

የትግራይ ክልል ለምርጫ የጀመረውን ኢ-ህገ መንግስታዊ እንቅስቃሴ እንዲያቆም የፌዴሬሽን ም/ቤት አሳሰበ

By Feven Bishaw

July 31, 2020

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 24፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የትግራይ ክልል መንግስት ምርጫ ለማካሄድ የጀመረውን ኢ-ህገ መንግስታዊ እንቅስቃሴ በአፋጣኝ እንዲያቆም ሲል የፌዴሬሽን ምክር ቤት አሳሰበ፡፡

ምክር ቤቱ ለትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት በላከው ደብዳቤ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ምክንያት ስድስተኛውን ሀገራዊ ምርጫ ማካሄድ እንደማይችል ያቀረበውን ሪፖርት መነሻ በማድረግ የሕገ መንግስት ትርጉም እንደተሰጠበት አስታውሷል፡፡