አዲስ አበባ ፣ሐምሌ 25 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ዛሬ በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ቢሮ በህግ ጥላ ስር የሚገኙ ተጠርጣሪዎች የሚገኙበትን ሁኔታ እና የተጠርጣሪዎችን አያያዝ በማረፊያቸው ተዘዋውረው ተመለከቱ።
ጠቅላይ አቃቤ ህጓ በህግ ጥላ ስር የሚገኙት አቶ ጃዋር መሃመድ፣ አቶ በቀለ ገርባ እና አቶ እስከንድር ነጋን ጨምሮ ከእነርሱ ጋር የሚገኙ ተጠርጣሪዎችን የሰብዓዊ መብት አያያዝ የሚገኝበትን ሁኔታ ነው ተዘዋውረው የተመለከቱት።