የሀገር ውስጥ ዜና

የብልጽግና ፓርቲ ለክልልና ከተማ አስተዳደር የፓርቲው ጽ/ቤቶች የኮሮና ቫይረስ መከላከያ ቁሳቁሶችን አስረከበ

By Feven Bishaw

August 03, 2020

አዲስ አበባ፣ ሃምሌ 27፣ 2012(ኤፍ ቢ ሲ) የብልጽግና ፓርቲ ለክልልና ከተማ አስተዳደር የፓርቲው ፅህፈት ቤቶች የኮሮና ቫይረስ መከላከያ ቁሳቁሶችን አስረከበ፡፡

ዋና ጽህፈት ቤቱ 98 ሺህ ማስኮችንና 24 የሙቀት መለኪያዎችን ነው ለክልልና ከተማ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ሃላፊዎች ያስረከበው፡፡