የሀገር ውስጥ ዜና

በአቶ በቀለ ገርባ ላይ በቂ ምርመራ ማድረጉንና የቀዳሚ ምርመራ መዝገብ መከፈቱን መርማሪ ፖሊስ ገለፀ

By Tibebu Kebede

August 04, 2020

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 28፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኦፌኮ አመራር የሆኑት አቶ በቀለ ገርባ በዛሬው እለት በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርበዋል።

በዚህም አቶ በቀለ ገርባ የእርስ በእርስ ግጭት ወንጀል በማነሳሳት የተጠረጠሩ መሆናቸውን ተከትሎ መርማሪ ፖሊስ በቂ ምርመራ ማድረጉን በመግለፅ የቀዳሚ ምርመራ መዝገብ መክፈቱን ለችሎቱ አስረድቷል።